1. ሰሞኑን በተሳተፍኩበት አንድ ውይይት ላይ ለአደንዛዥ
ዕፅ ሱስ መስፋፋት ምክንያቱ የትውልዱ የሞራል ዝቅጠት ነው የሚል ሃሳብ ካንድ ምሁር ቀርቦ አሳፋሪ ክርክር አድርገንበታል፡፡ ሱሰኝነትን
ከሞራል ዝቅጠት ጋር የሚያይዝ “ምሁር” በዚህ ዘመን ማግኘት ከባድ ነበር፤ አገሪቱ ብርቅዬ እንስሳትን ጨምሮ ብዙ ብርቅዬ ነገሮች
ስላሉባት ግን ብዙ አልተደነኩም፡፡
2. ከወራት በፊት ራሱን ባጠፋው የኔሰው ገብሬ አሟሟት
ዙሪያ በተለያዩ ፀሃፍትና ምሁራን የቀረቡ ሃሳቦችም ከፖለቲካ ብሶት በስተቀር የሚጨበጥ የሞራል ትንታኔ ማቅረብ አልቻሉም፡፡ ብዙዎች
በየኔሰው ጤና ዙሪያ ከጥርጣሬ እንዳልፀዱ በቅርብ የገጠመኝ ሰው እማኜ ነው፡፡
3. ቀደም ብሎ በጁፒተር ሆቴል ተካሄዶ የነበረውን
የHomosexuals ስብሰባን በተመለከተ የተለያዩ ፀሃፊዎች የፃፉት ጫጫታን እንዲሁም በጉዳዩ ላይ ክርክር ለማድረግ አለመፍቀዳቸውን
ታዝቤአለሁ፡፡
4. ሰሞኑን ደግሞ Tsegaye
Hailesilassie በፌስቡክ ሰሌዳው ላይ በAtheists ላይ የሰነዘረውን ጉንተላ ተከትሎ የተደረጉት ክርክሮች በJudo-christian
እይታ ተፅዕኖ ስር የወደቁና የፅንሰ-ሃሳብ ዕጥረት የሚታይባቸው ሆነው አግኝቻቼዋለሁ፡፡
ይህ ሲጠራቀም ኢትዮጵያውያን ምሁራንና ፀሃፍት
ከፖለቲካ ባሻገር ትርጉም የሚሰጥ ሃሳብ ማመንጨት አይችሉም ወይ የሚል ብሶት ተናነቀኝ፡፡ ብሶቴን ተጋሩኝ!